ልጥፎች

የኢትዮጵያ ወጣት ዕጣ፡ ከሞት ሽሽቶ ወደ ሞት!

ምስል
  “ልጄ ትሞትብኛህ፣ ጊዜው እሰኪያልፍ አዲስ አበባ ሄደህ ተደበቅልኝ” ይህ አንድት ኢትዮጵያዊት እናት ልጇን ከሞት ለማሸሽ እንባ እየተናነቃት የተናገረችው ቃል ነው፡፡ ይህን ቃል ከእናቱ አንደበት የሰማው ወጣት ደግሞ ቤተሰቦቹን ለመጠየቅ ወደ ትውልድ ቀዬው የተመለሰ ነው፡፡ አንድ ወጣት የናፈቁትን ቤተሰቦቹን ለመጠየቅ ከመቀሌ ወደ ትውልድ አካባቢው ደብብ ትግራይ ይጓዛል፡፡ ወጣቱን በጉዞ ላይ እያለ እናቱ እንዴት በደስታ አቅፋ እንደምትቀበለው እያሰበ ምን በደርስኩ ብሎ ልቡ ቀድሞ ካደገበት ቀዬ ደርሷል፡፡ የጠበቀው ያ ማየት የጠበቀው የእናቱ በደስታ የፈካ ፊትና የስስት እቅፍ አይደለም፡፡ ወጣቱ ከሰባት ወራት በኋላ ወደ ትውልድ መንደሩ ሲደርስ እንደጠበቀው እናቱ በደስታ አቅፋ እንድትቀበለው እየጠበቀ ቢሆንም፣ ያልተለመደና ያልጠበቀው ነገር ይገጥመዋል፡፡ ወጣቱ ከናፈቃት እናቱ ፊት ላይ በተያዩ ቅጽበት ያነበበው ምስል ከጠበቀው በተቃታኒ እጅግ የመከፋት ስሜት ሆነብት፡፡ ወጣቱ ያልጠበቀውን የእናቱን መከፋት ገና ሳያቅፋት እንደተመለከተ ወደ አእምሮው የመጣው አንድ በጎ ያልሆነ መርዶ እንደሚነገረው ነው፡፡ በናፈቃት እናቱ የተከፋ ፊት አቀባብል የተደረገለት ወጣቱ የመጀመሪያ ጥያቄው “እናቴ አለፈች?” የሚል ነበር፡፡ እናቱ የተከፋ ፊቷን በፈገግታ ለመሸፈን እየቃጣት ለልጇ ጥያቄ መልስ ሳትሰጥ “ልጄ ምነው አሁን መጣህብኝ?” በማለት የራሷን ጥያቄ አስከትላ አይን አይኑን አትኩራ ተመለከተች፡፡ ልጅ ባልጠበቀው ሁኔታ ግራ ተጋብቶ የአያቱን መሞት እንደሚረዳ እየጠበቀ እናቱ ወደቤት ይዛው ገብታ እንዴት እንደሰነበተ በመጠየቅ ቡና መቁላት ጀመረች፡፡ እናት ቡናዋን እየቆላች ወደ ተረጋጋ የናፍቆት ጭውውት መግባቷን የታበው ልጅ፣ “ለምን መጣህብኝ” መባሉ እያሰ በማውጣት በማውረድ አእ...

የአብይ አህመድ እና ኢሳያስ አፈወርቂ መዋጊያዎች!

ምስል
ፋኖ፣ ኦነግ ሸኔና ብርጌድ   ንሓመዶም  ምንና ምን ናቸው? ዕለቱ መጋቢት 24 /2010 ዓ.ም ነው፡፡ ወቅቱም ኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ በፖለቲካ ውጥንቅጥ የተወጠረችበት፡፡ በዚህ ውጥረት “ከሰማይ የወረደው ሙሴ” የተባለላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መሪ ሆነው ብቅ አሉ፡፡ ዕለቱ ኢትዮጵያዊነት፣ ሰላምና ፍቅር አየር ተሞላ፡፡ ኢትዮጵያዊያንም በፌስታ ፈነደቁና ተሰፋም አደረጉ፡፡ እነ ኦነግና ግንቦት ሰባትን ያቀፈችውን ኤርትራም የሰላም ጥሪ ቀረበላት፣ ተቀበለችም፣ ታጣቂዎቹም አገር አማን ብለው ወደ አገራቸው ገቡ፡፡ እነሆ እንዲህ አንዲህ እያሉ ወራት ዓመታትንን እየወለዱ፣ የኢትዮጵያዊነት ሸንገላ ቃላቶች በአየር ላይ እየከሰሙ፣ የተወጠረው   የፍቅር ፌሽታ በአቅጣጫው እየኮሰመነ፣ ታጣቂዎችም ተከዳን ብለው ጦራቸውን ወደ መንግሥት ካዞሩ ሰነባበቱ፡፡ በጣት ቀለበት የታሰረው የኢሳያስና የአብይም ወዳጅነት እነሆ እንዳልነበረ ሆኖ ጦር መማዘዝ ብቻ ቆርቷቸዋል፡፡ ሁለቱ መሪዎች በአንድ መድረክ ላይ ቆመው ማንም አይለየንም እንዳላሉ፣ በጎሪጥ መተያየት ጀምረዋል፡፡ ነገሮች እንዳልነበር ሆነው ተከረባብተው ጠላት ያሉትን ኃይል ለመውጋት በጋራ የተሰለፉ አካላት በየፊናቸው ጎራቸውን ለይተው አዲስ ጥምረት ለመመስረት እየጠሯሯጡ ነው፡፡ አብይና ኢሳያስ ሲለያዩ በታጠቁ ኃይሎች በኩል ለመወጋጋት ጉድጓድ እየማሱ ነው የሚለው ወሬ አየሩን ሞልቶት ሰንብቷል፡፡ ነገሩ በወሬ ብቻ የሚቆም አለመሆኑን ከሁለቱም አገራት በኩል ምልክቶች ታይተዋል፡፡ አብይና ኢሳያስ ለጎንዮሽ ውጋት የሚመዙት ካርድ እንደማይቸገሩ ለማሳየት ጥረት እያደረጉ ነው፡፡   ኦነግ ሸኔ በድርድር፣ ፋኖን በሰፈር ሽምግልና ለመደለል ጥረት ያደረገው መንግሥት እጅ ሲያጥረው፣ የእ...

ኢትዮጵያን ማን ያሻግራት?

ምስል
  ኢትዮጵያን ማን ያሻግራት?   በጋዜጠኛ መርሻ ጥሩነህ በግራ በቀኝ ወጀብ በበዛበት ሁኔታ ቀናት ወራትን፣ ወራት ዓመታትን እየወለዱ ጊዜ ው  እየነጎደ ነው፡፡  ዓመቱ እጅግ ፈታኝ ዓመት ሆኖ ብቻ አላለፈም፣ ይልቁንም ለተተኪው ዓመት አዳሪ ችግሮችን አሸግሯል፡፡ በዚህ መሰል ወጀብ ውስጥ እያለፈች የምትገ ኘ ውን ኢትዮጵያ አሸጋሪ ትሻለች፡፡ ኢትዮጵያ ፈታኝ ወቅት ላይ እንደምትገኝ አሁን ላይ የገጠሟች ዘርፈ ብዙ ችግሮች ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ መሆኑን፣ ከኃይማኖት ተቋማት እስከ፣ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እስከ ፖለቲካ አዋቂዎች፣ ከማኅበረሰብ አንቂ እስከ ተርታው ማኅበረሰብ በየፊናቸው ያረጋገጡት ሀቅ ነው፡፡ ጥያቄው ኢትዮጵያን ማን ያሸግራት? የሚለው ነው፡፡ በተከታወዩ ጽሑፍ የ2015 አብይት ጉዳዮች ምን እንደነበሩና ኢትዮጵያን ማን ያሻግራት የሚሉትን ጉዳዮችን በወፍ በረር እንመለከታለን፡፡ የ2015 አበይት ጉዳዮች ምን ነበሩ? የተጠናቀቀው 2015 እንዴ አገር ለኢትዮጵያ፣ እንዴ ዜጋ ለኢትዮጵያን በብዙ ችግሮች ታጅቦ ያለፈ ዓመት እንደነበር፣ በዓመቱ የተከናወኑ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አበይት ጉዳዮች አመለካች ናቸው፡፡ ü   የሰሜኑ ጦርነት ማብቃት የሰሜኑ የኢትዮጵያ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ምምነት መሰረት ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ የእርስ በእርስ ጦርነት በኋላ ያበቃው፣ በተሸኘው 2015 ሁለተኛ ወር ላይ ነበር፡፡ ጥቅምት 23/2015 የፌዴራል መንግሥት እና ህወሓት በአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙበት ዓመት ሆኖ አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ በሰላም ስምምነቱ መሰረት ይፈጸማሉ በተባሉ ጉዳዮች ላይ አሁንም ውዝግበቶ መነሳታቸውን ቀጥለዋል፡፡ የሚነሱ...

ዳግማዊ ትግራይ በአማራ ላይ!

ምስል
ዳግማዊ ትግራይ በአማራ ላይ! በጋዜጠኛ መርሻ ጥሩነህ ከሚሊዮን ዜጎች እልቂት እስከ ሚሊዮች አርዛት፣ ከሚሊዮኖች መፈናቀልና ጉስቁልና እስከ ትሪሊዮን ብር ውድመት ያስከተለው፣ የትግራይ እርስ በእርስ ጦርነት ዛሬም በሌላ ተረኛ ሕዝብ ላይ ተደቅኗል የሚሉ ድምጾ ከሰሞኑ ከየአቅጣጫው በስፋት ተሰምተዋል፡፡ የእነዚህ ድምጾች መነሻ ከትግራዩ ጦርነት ማብቃት ማግስት በአማራ ክልል በፋኖ ታጣቀዎች እና በመንግሥት በካከል የተቀሰቀሰው ግጭት በሰላማዊ መንገድ ይፈታል ተብሎ ሲታሰብ ወደለየለት ውጊያ መሸጋገሩር ነው፡፡ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት ከዚህ ደቀም ትግራይ ክልል የሆነውን የሚደግም አካሄዶችን በግልጽ እያሳየ ነው። የአማራ ክልሉ የጸጥታ ችግር በትግራይ ጦርነት ወቅት የተፈጸሙ ተፊ ጥቃቶችና ጥፋቶች ሊስከተል እንደሚችል፣ አደባባይ የወጡ ማስረጃዎች ከወዲሁ ፍንትው ብለው እየታዩ ነው፡፡ በትግራዩ ጦርነት ጅማሮ ላይ የታዩ ፍረጃዎች፣ የክልል መንግሥታት የጦርነት ድጋፍ ዘመቻ፣ የእነ ዳቆን ዳንኤል ክብረትና መሰሎቹ የተለመደ ጦርነት የማቀጣጠል ተግባር፣ በከተሞች ጭምር የሚፈጸሙ ድሮን ጥቃቶች፣ የሰላማዊ ሰዎች ግድያ፣ አማራ ተወላጆች ጅመላ እስር፣ በፌዴራል መንግሥቱ በኩል በግልጽ ተጀምሯል። ያኔ በትግራዩ ጦርነት ዋዜማ ከመቀሌ አዲስ አበባ፣ ከአዲስ አበባ መቀሌ በብልጽግና እና በሕወሓት መካከል ሲዥጎደጎዱ የነበሩ የቃላት ጦርነቶችና እርስ በእርስ መፈራረጆች፣ ዛሬም በመንግሥት እና በአማራ ክልል በመንግሥት ላይ ባመጹ ኃይሎች መካከል በግልጽ ተጀምሯል፡፡ የዛሬን አያድርገው እና ያኔ በለውጡ ሰሞን ሕወሓት ከአዲስ አበባ ተነቅሎ፣ መቀሌ ሲመሽግ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድና መሰሎቻቸውን የፍረጃ ቃላት ተቀብለው በአደባባይ ሲያስተጋቡ የነበሩ የገዥው ብል...