ልጥፎች

ኢትዮጵያን ማን ያሻግራት?

ምስል
  ኢትዮጵያን ማን ያሻግራት?   በጋዜጠኛ መርሻ ጥሩነህ በግራ በቀኝ ወጀብ በበዛበት ሁኔታ ቀናት ወራትን፣ ወራት ዓመታትን እየወለዱ ጊዜ ው  እየነጎደ ነው፡፡  ዓመቱ እጅግ ፈታኝ ዓመት ሆኖ ብቻ አላለፈም፣ ይልቁንም ለተተኪው ዓመት አዳሪ ችግሮችን አሸግሯል፡፡ በዚህ መሰል ወጀብ ውስጥ እያለፈች የምትገ ኘ ውን ኢትዮጵያ አሸጋሪ ትሻለች፡፡ ኢትዮጵያ ፈታኝ ወቅት ላይ እንደምትገኝ አሁን ላይ የገጠሟች ዘርፈ ብዙ ችግሮች ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ መሆኑን፣ ከኃይማኖት ተቋማት እስከ፣ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እስከ ፖለቲካ አዋቂዎች፣ ከማኅበረሰብ አንቂ እስከ ተርታው ማኅበረሰብ በየፊናቸው ያረጋገጡት ሀቅ ነው፡፡ ጥያቄው ኢትዮጵያን ማን ያሸግራት? የሚለው ነው፡፡ በተከታወዩ ጽሑፍ የ2015 አብይት ጉዳዮች ምን እንደነበሩና ኢትዮጵያን ማን ያሻግራት የሚሉትን ጉዳዮችን በወፍ በረር እንመለከታለን፡፡ የ2015 አበይት ጉዳዮች ምን ነበሩ? የተጠናቀቀው 2015 እንዴ አገር ለኢትዮጵያ፣ እንዴ ዜጋ ለኢትዮጵያን በብዙ ችግሮች ታጅቦ ያለፈ ዓመት እንደነበር፣ በዓመቱ የተከናወኑ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አበይት ጉዳዮች አመለካች ናቸው፡፡ ü   የሰሜኑ ጦርነት ማብቃት የሰሜኑ የኢትዮጵያ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ምምነት መሰረት ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ የእርስ በእርስ ጦርነት በኋላ ያበቃው፣ በተሸኘው 2015 ሁለተኛ ወር ላይ ነበር፡፡ ጥቅምት 23/2015 የፌዴራል መንግሥት እና ህወሓት በአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙበት ዓመት ሆኖ አልፏል፡፡ ይሁን እንጂ በሰላም ስምምነቱ መሰረት ይፈጸማሉ በተባሉ ጉዳዮች ላይ አሁንም ውዝግበቶ መነሳታቸውን ቀጥለዋል፡፡ የሚነሱ...

ዳግማዊ ትግራይ በአማራ ላይ!

ምስል
ዳግማዊ ትግራይ በአማራ ላይ! በጋዜጠኛ መርሻ ጥሩነህ ከሚሊዮን ዜጎች እልቂት እስከ ሚሊዮች አርዛት፣ ከሚሊዮኖች መፈናቀልና ጉስቁልና እስከ ትሪሊዮን ብር ውድመት ያስከተለው፣ የትግራይ እርስ በእርስ ጦርነት ዛሬም በሌላ ተረኛ ሕዝብ ላይ ተደቅኗል የሚሉ ድምጾ ከሰሞኑ ከየአቅጣጫው በስፋት ተሰምተዋል፡፡ የእነዚህ ድምጾች መነሻ ከትግራዩ ጦርነት ማብቃት ማግስት በአማራ ክልል በፋኖ ታጣቀዎች እና በመንግሥት በካከል የተቀሰቀሰው ግጭት በሰላማዊ መንገድ ይፈታል ተብሎ ሲታሰብ ወደለየለት ውጊያ መሸጋገሩር ነው፡፡ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት ከዚህ ደቀም ትግራይ ክልል የሆነውን የሚደግም አካሄዶችን በግልጽ እያሳየ ነው። የአማራ ክልሉ የጸጥታ ችግር በትግራይ ጦርነት ወቅት የተፈጸሙ ተፊ ጥቃቶችና ጥፋቶች ሊስከተል እንደሚችል፣ አደባባይ የወጡ ማስረጃዎች ከወዲሁ ፍንትው ብለው እየታዩ ነው፡፡ በትግራዩ ጦርነት ጅማሮ ላይ የታዩ ፍረጃዎች፣ የክልል መንግሥታት የጦርነት ድጋፍ ዘመቻ፣ የእነ ዳቆን ዳንኤል ክብረትና መሰሎቹ የተለመደ ጦርነት የማቀጣጠል ተግባር፣ በከተሞች ጭምር የሚፈጸሙ ድሮን ጥቃቶች፣ የሰላማዊ ሰዎች ግድያ፣ አማራ ተወላጆች ጅመላ እስር፣ በፌዴራል መንግሥቱ በኩል በግልጽ ተጀምሯል። ያኔ በትግራዩ ጦርነት ዋዜማ ከመቀሌ አዲስ አበባ፣ ከአዲስ አበባ መቀሌ በብልጽግና እና በሕወሓት መካከል ሲዥጎደጎዱ የነበሩ የቃላት ጦርነቶችና እርስ በእርስ መፈራረጆች፣ ዛሬም በመንግሥት እና በአማራ ክልል በመንግሥት ላይ ባመጹ ኃይሎች መካከል በግልጽ ተጀምሯል፡፡ የዛሬን አያድርገው እና ያኔ በለውጡ ሰሞን ሕወሓት ከአዲስ አበባ ተነቅሎ፣ መቀሌ ሲመሽግ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድና መሰሎቻቸውን የፍረጃ ቃላት ተቀብለው በአደባባይ ሲያስተጋቡ የነበሩ የገዥው ብል...